እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ቀን የመላእክት አለቃ የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው። እርሱም በባቢሎን አገር ከነደደ እሳት ውስጥ በጨመሯቸው ጊዜ አናንያን አዛርያን ሚሳኤልን ያዳናቸው ነው።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአማልጅነቱ ይማረን ለዘለዓለሙ አሜን።
![](https://ca.eotcmk.org/site/wp-content/uploads/St.-Gebreal-806x1030.jpeg)
አርኬ
ሰላም ዕብል ኪያከ ክቡረ፤
ለስመ ዚአከ ገብርኤል እንዘ አነሥእ መዝሙረ፤
እግዚአብሔር መንበሮ ሰማየ ሰማያት ዘገብረ፤
ይትመሰል በአርአያከ አመ ጊዜ ሐወጸ ምድረ፤
እምነ መላእክት ኵሉ ስነከ አፍቀረ።
ስንክሳር ዘወርኃ ታኅሣሥ
(ሙሉ ታሪኩን ትንቢተ ዳንኤል 3፥1-ፍጻሜው ያንብቡ)