• እንኳን በደኅና መጡ !

    "

ካናዳ ማእከል 22ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በአካልና በበይነ መረብ አከናወነ፡፡

በማኅበረ ቅዱሳን የካናዳ ማእከል 22ኛ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን ከሐምሌ 24 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ/ም በብሪቲሺ ኮሎምቢያ ክፍለ ሀገር በሆነችዉ በቫንኮቨር ከተማ አካሄደ። ጉባኤውን ያከናውነው በአካልና በበይነ መረብ ነው፡፡ በጠቅላላ ጉባኤውም የዋና ማእከል ተወካይ የሆኑት ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም በበይነ መረብ ተገኝተው የማኅበረ ቅዱሳንን መልእክት በማስተላለፍ፣ የማኅበረ ቅዱሳን የ5 መሪ ዕቅድ አጋማሽ ግምገማ […]

… ከባለፈው የቀጠለ… የሰሙነ ሕማማት ዕለታት ስያሜ (ከኀሙስ – ቅዳሜ)

“ሐዋርያቲሁ ከበበ፥እግረ አርዳኢሁ ሐፀበ፤ኮኖሙ አበ ወእመ፤ወመሀሮሙ ጥበበ” ኀሙስ የሰሙነ ሕማማት ዕለተ ኀሙስ ስያሜ ጸሎተ ኀሙስ፣ የሕጽበተ እግር ቀን፣ የምሥጢር ቀን፣አረንጓዴው ኀሙስ፣ትዕዛዘ ኀሙስ፣ የሐዲስ ኪዳን ኀሙስ፥ የነጻነት ኀሙስ ይባላል። ጸሎተ ኀሙስ ፡- ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ጸሐፍት ፈሪሳውያን የአይሁድ ሊቀ ካህናት መጥተው እስኪይዙት ድረስ በጌቴ ሴማኒ በአትክልቱ ስፍራ ሌሊቱን ሲጸልይ ያደረበት ዕለት ነውና ጸሎተ ኀሙስ ይባላል። (ማቴ […]

የሰሙነ ሕማማት (የዕለታት ስያሜ) (ከሰኞ – ረቡዕ)

“እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም” ከሆሣዕና ዋዜማ ጀምሮ እስከ ትንሣኤ ያለው ሳምንት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ እግዚአብሔር ወልድ የሰውን ልጅ ለማዳን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ተወልዶ በፈቃዱ መከራ መስቀልን እንደተቀበለ “እርሱ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፤ ሕማማችንንም ተሸከመ፡፡›› (ኢሳ.53፥4‐6) በማለት ነቢዩ ኢሳይያስ የክርስቶስን ነገረ […]

ካናዳ ማእከል 21ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በኦታዋ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን እያከናወነ ይገኛል፡፡

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መመሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የካናዳ ማእከል 21ኛ ጠቅላላ ጉባኤ በኦታዋ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በአካልና በበይነ መረብ ከሐምሌ 25/2017 ዓ.ም ጀምሮ ጉባኤውን እያከናወነ ይገኛል። በጉባኤው የአብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች ፣አባቶች ካህናት፣ የማኅበሩ አባላት፣ አጋርና ደጋፊ አባላት እንዲሁም የተሳታፊ ልጆች፣ ወጣቶች በብዙ የተገኙበት ሲሆን ከጠቅላላ ጉባኤው በተጨማሪ በልዩ ሁኔታ ለወጣቶችና ለሕጻናት ለብቻ […]

ሐዊረ ሕይወት

ማኅበረ ቅዱሳን ካናዳ ማእከል የቶሮንቶ ንኡስ ማእከል ከሳውዝ ዌስት ኦንታሪዮ ንኡስ ማእከል ጋር በመተባበር ወደ ሐሚልተን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር አከናወኑ። የሕይወት ጉዞው የተከናወነው ለወላጆች፣ለወጣቶችና፣ለሕጻናት የተለያዩ  መርሐ ግብራትን በማዘጋጀት ነው።ለወላጆች የመዝሙር፣ የስብከተ ወንጌል፣የምክረ አበው መርሐ ግብራት የተከናወኑ ሲሆን።በምክረ አበው መርሐ ግብሩ ላይ ሊቀ ጠበብት ማኅቶት የሻው፣ መጋቢ ሐዲስ አክሊለ ብርሃንና ቀሲስ […]

“ለኢትዮጵያ ሰዎች ምግባቸውን ሰጠሃቸው፡፡” መዝ 73፡14

በዲ/ን አሰበልኝ ጨቡድ ውድ አንባብያን እንኳን ለቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ግንቦት 11 ቀን ኢትዮጵያዊው ሊቅ፣ማኅሌታይና የዜማ ደራሲ ቅዱስ ያሬድ የተሠወረበት ቀን ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን የመላእክትን ምግብ /ምስጋና/ እንደበሉ ቅዱስ ዳዊት ሲገልጽ “ለኢትዮጵያ ሰዎች ምግባቸውን ሰጠሃቸው” በማለት እንደተናገረ፡፡ ኢትዮጵያም ምግብ የተባለ የመላእክትን ምስጋና በሊቁ በቅዱስ ያሬድ አማካኝነት አግኝታለች፡፡ ቅዱስ ያሬድ ከአባቱ ከአብዩድ/ይስሐቅ/ ከእናቱ ከክርስቲና/ታውክልያ/ በ505 […]

ለእናቷ አንዲት ናት፤ለወለደቻትም የተመረጠች ናት፡፡ (መኃ 6፥9)

ለእናቷ አንዲት ናት፤ለወለደቻትም የተመረጠች ናት፡፡ (መኃ 6፥9) እንኳን ለእናታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ! እመቤታችንን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱሳን ከሆኑ ከኢያቄምና ከሐና የተወለደችበት ቀን ነው፡፡ አያቶቿና ወላጆቿ ንጹሐን፣ ቅድሳን እንደሆኑ ቅዱስ ዳዊት “መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው” /መዝ.86፥1/ በማለት መሥክሯል፡፡ ይህ ምስክርነት አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ ለኩነተ ሥጋ የመረጣት ቅድስት ድንግል ማርያም ወላጆቿ […]

“ኢየሱስም ከገሊላ ናዝሬት መጥቶ በዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡” ማር 1÷9

“ኢየሱስም ከገሊላ ናዝሬት መጥቶ በዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡” ማር 1÷9 ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድሰት ድንግል ማርያም በኅቱም ድንግልና ተጸንሶ በኅቱም ድንግልና ተወልዶ በተወለደ 40 ቀኑ ዕጉለ ርግብ ዘውገ ማዕነቅ ይዞ ወደ ቤተ መቅደስ በመግባት፣በዓመት ሦስት ጊዜ ለበዓል ኢየሩሳሌም በመውጣት ሕግ መጽሐፋዊን ሕግ ጠባያዊን እየፈጸመ “በበህቅ ልህቀ እንዘ ይትኤዘዝ ለአዝመድሁ እንተ […]

እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ!

እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ቀን የመላእክት አለቃ የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው። እርሱም በባቢሎን አገር ከነደደ እሳት ውስጥ በጨመሯቸው ጊዜ አናንያን አዛርያን ሚሳኤልን ያዳናቸው ነው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአማልጅነቱ ይማረን ለዘለዓለሙ አሜን። አርኬሰላም ዕብል ኪያከ ክቡረ፤ለስመ ዚአከ […]

ማስታወቂያ

ከበረከቱ በመካፈል የማኅበሩን አገልግሎት እንዲደግፉ ኃላፊነትዎን ይወጡ።

ሐዊረ ሕይወት

የፌስቡክ ልገሳ

የተለያዩ መንፈሳዊ ትምህርቶችን በየቤታችን ለማግኘት ምክንያት የሆነውን የማኅበራችንን ሚዲያ በመደገፍ የበኩላችንን አስተዋጽኦ እናበርክት::

ማኅበረ ቅዱሳን ካናዳ ማዕከል::